በትግራይ ክልል ትግራይ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ግዥና ንብረት አስተዳደር ለ2012 በጀት ዓመት የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በአገር አቀፍ ግልፅ ጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ህዝብ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት
  • የ2012 ዓም እድሳት የተደረገለት የንግድ ስራ ፍቃድ፣ የአቅራቢነት ምዝገባ ሰርቲፍኬት፣ የቫት ምዝገባ ምስክር ወረቀት የካቲት ወር የቫት ዲክላሬሽን ፣ቲን ምዝገባ ወረቀት ማቅረብ አለባቸው
  • መስፈርቶቹን የሚያሟሉ ሁሉም ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከትግራይ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ የግዥና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 105 ከ29/7/2012 ዓ/ም እስከ 13/8/2012 ዓ/ም 11:30 በስራ ሰዓት ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።

ጨረታው የሚዘጋበት የመጨረሻ ቀን በ14/8/2012 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በተመሳሳይ ቀን

 በ13/8/2012 ዓ/ም ጠዋት 4:30 ሰዓት ቢሮ ቁጥር 105 ይከፈታል።




  •      የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና/ በተጫራቾች ምርጫ መሰረት ከሚከተሉት አንዱ ሊሆን ይችላል ፡፡
  • ሀ. በህግ ከታወቀ በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (unconditional bank guarantee)
  • ሊ. በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና
  • ሐ. በታወቀ ባንክ የተረጋገጠ የገንዘብ ክፍያ ማስያዣ (CPO) ሆኖ ብር 120,000.00(አንድ መቶ ሃያ ሺ ብር ) ማቅረብ አለባቸው::
  • የሚያስፈልግ የዶክመንት ብዛት ቴክኒካል ኦርጅናል ዶክመንት ከነ 2 ኮፒ እና ፋይናንሻል ኦርጅናል ዶክመንት ከነ 2 ኮፒ ለየብቻቸው በፖስታ በማሸግ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
  • ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ውስጥ ያሉትን ቅፆች በትክክል በመሙላት፣ በያንዳንዱ የሰነዱ ገፅ ፊርማ እና የድርጅቱን ማህተም ማድረግ አለባቸው።
  • ድርጅታችን ትግራይ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ይህ ጨረታ በማንኛውም ጊዜ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ይሁን በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ---------------ትግራይ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ

ቢሮ ቁጥር -----105 ግዥና ንብረት አስተዳደር ስልክ ቁጥር ----- 0342406380

በትግራይ ክልል ትግራይ መገናኛ. ብዙሃን ኤጀንሲ ግዥና ንብረት አስተዳደር

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo