የመቀሌ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት የሚያገለግል የውሃ ጥራት ላቦራቶሪ ሪኤጀንትስ፣ ኬሚካልስ እና ሶሉሽንስ ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛትይፈልጋል

የመቕለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት
  • ጨረታዉ የወጣበት ቀን :  17/7/2012
    ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን : በ30ኛዉ ቀን 4:00 ሰዓት
    ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን : በ30ኛዉ ቀን 4:30 ሰዓት
    ላቦራቶሪ ሪኤጀንትስ፣
  • ኬሚካልስ እና ሶሉሽንስ ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ በጨረታው መሣተፍ ለምትፈልጉ ተጫራቶች ጥሪውን ያቀርባል፡፡ 
  1. የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው 
  2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ 
  3. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክሜንት ከደጋፊ ሥራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ፡፡ 
  4. ጨረታ ዶክሜንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሣጥኑ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ30ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራች ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ 
  6. 6.ሁሉም ተጫራቾች 20,000.00 የጨረታ ማስከበሪያ በCPO፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና፣ በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና፣ ጥሬ ገንዘብ፣ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትዕዛዝ፣ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ 
  7. ተጫራቹ ካሁን በፊት በፅ/ቤታችን ተወዳድሮ ያሸነፈው ንብረት 100% ካላስገባ ካላቀረበ/ በዚህ ጨረታ መወዳደር አይችልም፡፡ 
  8. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው፡፡ 
  9. በዶክሜንቱ ከተሰጠው ስፔስፊኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም፡፡ 
  10. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO፣ በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበሪያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ውል አስሮ በዶክሜንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል 
  11. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግሥት ግዢ እንዳይሣተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ 
  12. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም፡፡ 
  13. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው፡፡ 
  14. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 
  15. የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት 
  • 15.1 ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም 
  • 15.2 ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል፡፡ 

16. ጽ/ቤቱ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

  •                                  አድራሻ፡-ትግራይ መቐለ ስልክ ቁጥር 0344407335/0914755845 

የመቐለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo