በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት፣እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ በ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት ለማከናወን ካቀዳቸው ግዥዎች ውስጥ የዶክመንታሪ ፊልም ዝግጅት እና የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ግዥ በአገር ውስጥ ገበያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

አፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የእንስሳት፤እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ
  • የዶክመንታሪ ፊልም ዝግጅት እና
  • የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ግዥ በአገር ውስጥ ገበያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። 

 ተጫራቶች ግዴታ ማሟላት ያለባቸው የቅድሚያ መወዳደሪያ መስፈርቶች ማለትም፡-



  • 1.1 በዘርፉ የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያለው 
  • 1.2 የንግድ ፍቃድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ያለው 
  • 13 የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ 
  • 1.4 የግብር ክፍያ መለያ ቁጥር (Tin No) ያለው 
  • 1.5 ሲ.ፒኦ ማስያዝ አለበት እና 
  • 1.6 የጨረታ ሰነድ ግዥ የፈጸመ 

2. በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታውን ሰነድ ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት፣ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ በግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ ዳይሬከቶሬት ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡ 

3. ተጫራቾች በእያንዳንዱ በሚያቀርቡት የጨረታ ሰነዶች ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪል ፊርማና ማህተም ማኖር ይኖርባቸዋል፡፡ 

4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid Bond) ለውድድር የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 1% በሲፒኦ (CPO) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማስያዝ እና የዘሩ ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታው ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ከተሸነፉ ለዋስትና ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትናና እንዲሁም ናሙና የጨረታው ውጤት ታውቆ ውል ከተፈራረሙ በኋላ ወዲያውኑ ማስከበሪያ ይመለስላቸዋል፡፡ 

5. ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ማንኛውም ተጫራች የሚያቀርቡት የውድድር ጥያቄ መ/ቤቱ አይቀበልም፡ 

6. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን በ15ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ የሚዘጋ ሲሆን በዕለቱ 4፡30 ሰዓት በአፋር ብሔራዊ ከልላዊ መንግስት የእንስሳት፣ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል ነገር ግን 15ኛው ቀን የስራ ቀናት ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀናት የሚከፈት ይሆናል፡፡ 

7. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

8. ለተጨማሪ መረጃ በቢሮ ግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ክፍል ቢሮ ቁጥር 108 በአካል በመገኘት ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡ 

በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት 

የእንስሳት፣እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ /ሠመራ/ 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo