የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜን ዕዝ ጠ/መምሪያ የ20ኛ ክ/ጦር ለህሙማን ማጠናከሪያ የሚውል ወተት እና ለመኖሪያ ቤት ግንባታ/የኮንስትራክሽን/የሚውል ማቴሪያሎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

በሀገር መከላከያ ሚኒስትር የሰ/ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ
  1. ለህሙማን ማጠናከሪያ የሚውል ወተት
  2. ለመኖሪያ ቤት ግንባታ/የኮንስትራክሽን/የሚውል ማቴሪያሎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
  1. ተጫራቾች ለወጣው ጨረታ በዚህ የስራ ዘርፍ የተሰማሩ፣ ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ የዘመኑን ግብር የከፈሉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ እና የግብር ከፋይ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፣ የአቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፊኬት ያላቸው ተጫራቾች ይጋብዛል።
  2. ለጨረታ ማስከበሪያ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው የፋይናንስ ተቋማት CPO ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. ዕቃዎቹ እንትጮ መመን/ መኖሪያ ጊቢ እና አክሱም/ ዓዲ እክል መኖሪያ ቤት ጊቢ በራሱ ትራንስፖርት ማቅረብ የሚችል።
  4. ተጫራቾች ማስረጃ በየራሳቸው ፎቶ ኮፒ አድርገው ማቅረብ የሚችሉ ዋናውን ሲጠየቁ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለበት
  5. የጨረታ ሰነድ ከመጋቢ 05/07/2012 ዓ/ም እስከ 19/07/2012 ዓ/ም ዘወትር በስራ ሰዓት ከ20ኛ ክ/ጦር ግዥ ዴስክ ቢሮ 100 ብር /አንድ መቶ ብር/ በመግዛት መውሰድ ይችላሉ።
  6. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዕለ በ19/07/2012 ዓ/ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ጨረታው ይከፈታል፡፡
  7. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

NB፡- ለበለጠ መረጃ በስ/ቁጥር፡-0342455429/ 0987394858/0914303911/ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

  • አድራሻ
  • ክልል……...……… ትግራይ
  • ዞን………...….……ምስራቃዊ
  • ወረዳ……..…….…ጋ/አፈሹም
  • ቦታ………..…አዲ-ግራት የ20ኛ ክ/ጦር ካምፕ

የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜን

ዕዝ ጠ/መምሪያ የ20ኛ ክ/ጦር

መምሪያ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo