የትግራይ ክልል ከተማ ልማት ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኮምፒውተርና ተዛማጅ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ከተማ ልማት ንግድና ኢንዱስትርን ቢሮ
  1. ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ቀን : 4/7/2012
    ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን : 16ኛዉ ተከታታይ ቀን ከቀኑ 8:00 ሰዓት
    ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን : በ16ኛዉ ተከታታይ ቀን ከቀኑ 8:30
    በዘርፉ 2012 ዓ/ም የታደሰ አቅራቢነት ማቅረብ የሚችል
  2. በዘርፉ 2012 ዓ/ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ ቫት ተመዝጋቢ የሆነ የታህሳስ 2012 ዲክለር ያደረጉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
  4. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ናምበር ማቅረብ የሚችል
  5. ተጫራቾች የጨረታው ሰነድ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 16 ተከታታይ ቀናት ከትግራይ ክልል ከተማ፣ ልማት ቢሮ 1ኛፎቅ ቢሮ ቁጥር 59 የማይመለስ ብር 100.00 አንድ መቶ ብርበመክፈል መውሰድ ይችላሉ
  6. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 16ኛው ተከታታይ ቀን ከቀኑ 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 830 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በትግራይ ክልል ከተማ ልማት ቢሮ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 59 የሚከፈት መሆኑን እየገለፅን ተጫራቾች ባለመቅረባቸው የማይከፈት ሰነድ የለም
  7. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000,00 አንድ መቶ ሺህ ብር በCPO ማስያዝ ይኖርባቸዋል
  8. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነድ ዋጋ ኦርጅናል አንድ ኮፒ አንድ ለየብቻው በታሸገ ኢንቨሎፕ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 16 ተከታታይ ቀናት እስከ 8:00 ሰዓት ትግራይ ክልል ከተማ ልማት፣ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 59 በማቅረብ ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ተወዳዳሪዎች የሚያቀርቡት ሰነድ ከስርዝ ድልዝ የፀዳና በእያንዳንዱ ገፅ ማህተምና ፊርማ መኖር አለበት።
  10. ሰነድ ጨረታ በሙሉም ሆነ በከፊል ማስቀረት ከጨረታ ውጪ ያደርጋል፡፡
  11. ተጫራቾች ሰነድ ላይ የተዘረዘሩትን ዕቃዎች አሸናፊ ከሆኑት ውል ከታሰረበት በሰላሳ ተከታታይ ቀናት እቃውን ማስገባት የሚችል፡፡
  12. ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር :-034-240-01-29 ወይም 03-44-40-89-73

ፋክስ ቁጥር 0344 415859

አድራሻ -ትግራይ ክልል ከተማ ልማት ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ /መቐለ/

የትግራይ ክልል ከተማ ልማት ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo