የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ጋብዮን፣ Crawler Bulldozer፣Hydraulic Excavator፣ ኤሌክትሮኒክስ /IT/ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ
  • ሎት  1 ጋብዮን
  • ሎት  2 1. Crawler Bulldozer
  •          2. Hydraulic Excavator
  • ሎት 3 ኤሌክትሮኒክስ /IT/ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፤

በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ዶኩሜንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ጀምሮ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መወሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፤ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል፡-

  • የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የVat ሰርተፍኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (Tin) እና ያለፈው ወር ቫት (Vat) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት፣
  • ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው፤
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዝብ በCPO አሠርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
  • ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበት የዕቃዎች ብዛት እስከ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፤
  • ጨረታው መጋቢት 22 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
  • ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- በስልክ ቁጥሮች 0344403663/ 0344404346

ወይም በፋክስ ቁጥር 0344409971/0344403663 መጠየቅ ይቻላል፡፡

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo