የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2012 ዓ/ም በጀት ዓመት የሚያገለግል ሳርፌስ ፓምፕ ከነ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስፔር ግር፣ እወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል

የመቕለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት
  1. የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው፡፡ 
  2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲከለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ፤ 
  3. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ 200.00(ሁለት መቶ) በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶከሜንት ከደጋፊ ሥራ ሂደት ግዢ ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 ሙግዛት ይችላሉ፡፡ 
  4. ጨረታ ዶክሜንቱን ማስገባት የሚቻለው ቢጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 2012 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ። 
  5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 15ኛው ቀን 2012 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ተጫራች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 
  6. ሁሉም ተጫራቶች 120,000.00 የጨረታ ማስከበርያ በCPO ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና፣ በማይሻር ሌተር ኦፍ ከሬዲት የቀረበ ዋስትና፣ የጥሬ ገንዘብ ፣ የተረጋገጠ ቼከ ወይም የከፍያ ትዕዛዝ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል። 
  7. ተጫራቹ ከአሁን በፊት በፅ/ቤታችን ተወዳድሮ ያሸነፈው ንብረት 100% ካላስገባ (ካላቀረበ) በዚህ ጨረታ መወዳደር አይችልም፡፡ 
  8. ተጫራቹነጠላ ዋጋናየጠቅላላ ዋጋበግልጽማስቀመጥ አለበት፡፡ በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው። 
  9. በዶከሜንቱ ከተሰጠው ስፔስፊኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም። 
  10. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በ CPO፣ በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበርያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶኩሜንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል፡፡ 
  11. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛበት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጪ እንደሚሆንና በመንግሥት ግዥ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ፡፡ 
  12. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣው የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም። 
  13. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው፡፡ 
  14. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደአስፈላጊነቱ ከያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  15. የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት፣ 
  • 15.1 ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም 
  • 15.2 ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል፡፡ 

16. ፅ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

አድራሻ ፡- ትግራይ መቐለ 

መቐለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት 

ስልክ ቁጥር፡- 0344407335 /0914755845 

የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo