የሰቲት ሁመራ ውሃና ፍሳሽ ጽ/ቤት ከዚህ በታች የተዘረዘሩ የተለያዩ መጠን ያላቸው የውሃ ትቦና መገጣጠሚያ፣ ፓምፓች፣ ዌልዲንግ ማሽን፣ ግራይንደር ማሽን፣ ላፕቶፕና የኮምፒዩተር እቃዎች፣ ፎቶ ኮፒ ማሽንና፣ ፕሪንተር፣ አይሲ፣ ስቴሽነሪ የፅዳት መገልገያዎች፣ ማውንቴን ሳይከል፣ ወንበሮች ሽልፎችና ጠረጴዛዎች፣ ሌሎችም በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

የሰቲት ሁመራ ውሃና ፍሳሽ ጽሕፈት ቤት
  • የተለያዩ መጠን ያላቸው የውሃ ትቦና መገጣጠሚያ፣
  • ፓምፓች፣
  • ዌልዲንግ ማሽን፣
  • ግራይንደር ማሽን፣
  • ላፕቶፕና የኮምፒዩተር እቃዎች፣
  • ፎቶ ኮፒ ማሽንና፣ ፕሪንተር፣
  • አይሲ፣ ስቴሽነሪ
  • የፅዳት መገልገያዎች፣
  • ማውንቴን ሳይከል፣
  • ወንበሮች ሽልፎችና ጠረጴዛዎች፣ ሌሎችም በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

በዚህ መሰረት የዚህ የግልፅ ጨረታ መስፈርት የምታሟሉ ተጫራቾች እንድትወዳደሩ በክብር እንጋብዛለን ። 

1 ጨረታ የሚከፈትበት የሚዘጋበት እንዲሁም ጨረታ ሰነድ የሚገኝበት ሰቲት ሁመራ ውሃና ፍሳሽ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 07 ነው። 

2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ የማይመለስ 50 ብር በመክፈል ሰቲት ሁመራ ውሃና ፍሳሽ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 07 መውሰድ የምትችሉ መሆኑ። 

3. የጨረታ ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ ወይ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም በCPO ማቅረብ የምትችሉ መሆን አለበት። 

3.1 የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ለ የውሃ ትቦና መገጣጠሚያ 7,000 ብር /ሰባት ሺ ብር/ 

3.2 ለኤሌክትሮ መካኒካል እቃዎች (ፓምፖችና ዌልዲንግ ማሽኖች) - 20,000 ብር /ሃያ ሺ ብር/ 

3.3 ለፎቶ ኮፒ፣ፕሪንተር፣ላፕቶፕና የኮምፒዩተር እቃዎች -5,000 ብር /አምስት ሺ ብር/ 

3.4 ለአይሲ /air condition/ - 3,000 ብር /ሶስት ሺ ብር/ 

3.5 ለፅህፈት መሳሪያ /stationary/ - 4000 ብር /አራት ሺ ብር/ 

3.6 ለአላቂና የፅዳት መገልገያዎች - 3,000 ብር /ሶስት ሺ ብር/ 

3.7 ለብስክሌት/ማውንቴን ሳይክሎች - 3,000 ብር /ሶስት ሺ ብር/ 

3.8 ለወንበር፣ ሸልፎችና ጠረጴዛዎች -5,000 ብር /አምስት ሺ ብር/ 

4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ መውሰድ የምትችሉት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ቀን 17/6/2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ሆኖ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት የምትችሉ መሆኑ። 

5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ በሁለት ኤንቨሎፕ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ማቅረብ ይኖርባቸዋል እነኝህ ኤንቨሎፖች አስተሻሽጋቸው አንድ አይነት የሆነ ዋናውንና ቅጂውን ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ 

6. ይህ ጨረታ በ17/6/2012 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ17/6/2012 ዓ/ም 5:00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ደግሞ ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት በሰቲት ሁመራ ውሃና ፍሳሽ ጽ/ቤት ይከፈታል፡፡ 

7. የጨረታው የአከፋፈት ስርአት ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባለመገኘታቸው ሊቆም አይገባም፡፡ 

8. ስርዝ ድልዝ ያለው የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡ 

9. በጨረታ ሰነድ በእያንዳንዱ ሰነድ ላይ ማህተምና ፊርማ መኖር አለበት፡፡ 

10. ጽህፈት ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

11. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0344481963 /0914741334/ 0919747273 ደውለው መጠይቅ ይችላሉ። 

የሰቲት ሁመራ ውሃና ፍሳሽ

ጽ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo