የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ኤሌክትሮኒክስ እና ልዩ ፍላጎት የትምህርት መርጃ መሳሪዎች በብሄራዊ ግልፅ ጨረታ አቅራቢዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የኣፋር ትምህርት ቢሮ
  • ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ቀን  : 5/5/2012
    ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን  : ለ15 ተከታታይ ቀናት
    ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን  : 16ኛዉ ቀን በ300 ሰዓት
  • ሎት 1 ኤሌክትሮኒክስ
  • ሎት 2 ልዩ ፍላጎት የትምህርት መርጃ መሳሪዎች በብሄራዊ ግልፅ ጨረታ አቅራቢዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፣
  2. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  3. በሚሳተፉበት አቅርቦት ጨረታ ክፍል አግባብ ካለው የመንግስት መ/ቤት ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀ የአገልግሎት አቅርቦት እንደሚሰጡ የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 ( ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ሠመራትም/ቢሮ ቁጥር 6 የጨረታውን ሰነድ በመግዛት የሚወዳደሩበትን ሀሳብ እና ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነዶችን በመለየት በ2 ኮፒ ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋ 2% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፣
  7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጂዎች ማለትም ዋና እና ቅጂ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ትምህርት ቢሮ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ዳሬከቶሬት ከፍል ቢሮ ቁጥር 5 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
  8. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በትምህርት ቢሮ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 6 በ16ኛው ቀን በ3፡00 ሠዓት ይከፈታል፡፡
  9. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣
  10. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ተጫራች ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 5 በስልክ ቁጥር 033-666-0125/0920009109 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo