የትግራይ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ኤጀንሲ ለ2012 የበጀት ዓመት ለክልሉ ኤጀንሲና በክልሉ ለሚገኙ የወረዳ ሞተር ሳይክሎች፣ ለኤሌክትሮኒክስ፣ ፈርኒቸር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ገጠር መሬት የኣካባቢ ጥበቃ ኣጠቃቀምና ኣስተዳደር ኤጀንሲ

ሞተር ሳይክሎች፣ ለኤሌክትሮኒክስ፣  ፈርኒቸር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ።

በዚህ መሰረት በጨረታው መወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራች ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች በማሟላት ማቅረብ ይኖርበታል።

1. ተወዳዳሪዎች

በዘርፉ የ2012 ዓ/ም የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው

VAT ተመዝጋቢዎች መሆናቸውን ማስረጃ የሚያቀርቡ

የሐምሌ/የነሐሴ ወር የቫት ዲክለራስዮን ያላቸውና ማስረጃ የሚያቀርቡ፣

ቲን ነምበር ያላቸውና ማስረጃ የሚያቀርቡ

በክልል ፋይናንስ ይሁን በፌዴራል የመንግስት ግዢ በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡና የ2012 ዓ.ም የታደሰ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት የሚያቀርቡ፣

2. ተጫራቾች የጨረታው ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ

ለሞተር ሳይክል ብር 5000 /አስራ አምስት ሺ ብር/

ለኤሌክትሮኒክስ ብር 10000 ብር /አስር ሺ ብር/

ለፈርኒቸር ብር 10000 ብር/አስር ሺ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ፣ በጥሬ ገንዘብ ወይም ሰርቲፋይድ ቼክ

2 በትግራይ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ኤጀንሲ ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝር መመሪያ ሰነድ የማይመለስ ብር 50.00 /ሃምሳ ብር/ በመክፈል ከግዢና ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት በመውሰድ ዋጋ ማቅረቢያ ሰነዶቻቸውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከ04/05/2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 19/05/2012 ዓ/ም ድረስ በስራ ሰዓት ለክልሉ የአካባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ኤጀንሲ ፖሳቁ 1234 በአድራሻ በመላክ ወይም በግንባር በመቅረብ በኤጀንሲው ግዢና ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር ይችላሉ።

ጨረታው 16ኛው ቀን 19/05/2012 ዓም 8:30 ሰዓት ከታሸጉ በኋላ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የተሻለ ሲሆን ባይገኙም 900 ሰዓት በክልሉ የአካባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ኤጀንሲ ይከፈታል፡፡

4. አሸናፊዎች ላሸነፉት ዋጋ ውል የማሰር /የመግባት ግዴታ አለባቸው። በገቡት ውል መሰረትም ይፈፅማሉ። በገቡት ውል ሳይፈፅሙ የቀሩ በእያንዳንዱ ቀን ካስያዙት የውል ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋ 2.1 % በመቀጣት ገቢ እንዲያደርጉ ይደረጋል ወይም በህግ ይጠየቃሉ፡፡

5. ተጫራቶች በቀረበው ጨረታ ሰነድ አስተያየት/ጥያቄ ካለዎት ከጨረታ መክፈቻው ከ5 ቀን በፊት ማቅረብ ይችላሉ በጨረታ ሰነዱ ስርዝ ወይም ድልዝ ካለበት ተቀባይነት አይኖረውም ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ለሚመጣ ጥያቄ ኤጀንሲው መልስ ለመስጠት አይገደድም፡፡

6. የሞተር ሳይክል ተወዳዳሪዎች ፋይናንሻል ዶክመንት ለብቻው ቴክኒካል ዶክመንት ለብቻው አሽገው ማቅረብ አለባቸው፡፡

7.ኤጀንሲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

8. ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ለ45 ቀን ዋጋው ፀንቶ ይቆያል።

9. ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0344417104 ደውለው መጠየቅ ይቻላል።

የፖ.ሣ ቁጥር ---1234

ስልክ ቁጥር ---- 0344-417104

ፋክስ ቁጥር --------- 0344-411697 መቐለ

የትግራይ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ኤጀንሲ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo