የከተማ ሰቲት ሑመራ ቤት ማዘጋጃ ጽሕፈት ቤት ለ2012 በጀት ዓመት ለተለያዩ አገልግሎት የሚውል የህትመት እቃዎች ፣ እላቂ ንብረቶች፣ የፅህፈት መሳርያዎች እና የጽዳት መሳሪያዎች፣ የኢሌከትሮኒክስ እቃዎች፣መኪና ሎደርና ሲኖትራክ/ እና የተሽከርካሪ መለዋወጫ ንብረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

የሰቲት ሑመራ መዘጋጃ ቤት

1.



ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የሚወጣበት ቀን 4/5/2012

ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን :  በ16ኛዉ ቀን  ከጠዋቱ 3:30

ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን :  በ16ኛዉ ቀን  ከጠዋቱ 4:00

 በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸወና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

2.ከመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ተመዝጋቢ የሆነ፡፡

3.ተጫራቾች ዮገብር ከፋይ ቁጥር Tin No./ ያላቸውና የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችል

4 የነሐሴ 2011 ዓ.ም ቫት ድክሌር ማስራጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችል።

5. ተጫራቾች ለተወዳደረበት ንብረት እንደ ንብረቱ ሁኔታ ከ6ት ወር /ስድስት ወር/ እስከ አንድ ዓመት ዋስትና መስጠት የሚችል፡፡

6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ እንደ ተጫራቹ ምርጫ በጥሬ ገንዘብ ወይም CPO ማስያዝ የሚችል፡፡

6.1 በሎት እንድ ያሉ ዝርዝር ዓይነት ንብረቶች የህትመት እቃዎች ፣ አላቂ ንብረቶች፣ የፅህፈት መሳርያዎች እና የጽዳት መሳሪያዎች ለሎት እንድ 5000 ብር /አምስት ሺህ ብር/

6.2 ለሎት ሁለት የኢሌከትሮኒክስ እቃዎች ለሎት ሁለት 10,0000 ብር / እስር ሺህ ብር/

6.3 ለሎት ሶስት (መኪና ሎደርና ሲኖትራክ/ እና የተሽከርካሪ መለዋወጫ /ስፔር/ለሎች ሶስት 35000 ብር በሠላሳ አምስት ብር ማስያዝ የሚችል፡፡

7. ተጫራቾች በጨረታ ያሸነፈው ዝርዝር ንብረት በራሳቸው ትራንስፖርት በትግራይ ክልል ምዕራባዊ ዞን ሰቲት ሑመራ ከተማ ማዘጋጃ ጽህፈት ቤት ማስረከብ የሚችሉ።

8.ተጫራቶች የሚጫረቱበት ዋጋ በግልፅ ኦርጅናል የጨረታ ሰነድ ላይ ሞልተው በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 15 ቀን ተከታታይ ቀናት ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

9. ጽህፈት ቤቱ፡ 20% በውል ላይ መጨመርም መቀነስም ይችላል። ጨረታ ሰነዱ በሁመራ ከተማ ማዘጋጃ ጽሕፈት ቤት ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት ቁጥር 10 በመምጣት 100.00 ብር በመከፈል ሙግዛት ይችላል።

10. መስሪያ ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ላይ ዋጋ ሞልቶ የድርጅቱ ህጋዊ ማህተምና ፣ ፊርማ ፣ አድራሻ ፣ ስም ስልክ ቁጥር አድርጎ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡

11.ተጫራቾች የሚጫረቱበት የጨረታ ሰነድ አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ለየብቻቸው ሆኖ መቅረብ ይኖርበታል በተጨማሪም ለየብቻው የታሸገ ሆኖ በእያንዳንዱ ፖስታ ላይ የተጫራቶች ህጋዊ ማህተምና ፊርማ እድራሻ፡ ስም ስልከ ቁጥር በማደረግ ሶስቱም ፖስታዎች በአንድ ትልቅ ፖስታ በማሸግ በትልቁ ፖስታ ህጋዊ ማህተምና ፊርማ ፣ አድራሻ ስም ስልክ ቁጥር በማድረግ ማቅረብ ይኖርበታል።

12. ተጫራቾች የሚሞሉት ዋጋ ላይ ስርዝ ድልን ካለው በጎኑ ፈርማ ማድረግ ይኖርባቸዋል ይህ ያለማድረግ ከጨረታ ውጭ ይሆናል።

13. የሚገዙ የግዢ ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዘዋል ይመልከቱት፡፡ ናሙና ለሚያስፈልጋቸው ንብረት በድርጅቱ ቅጥር ግቢ ቀርቦ በአካል ማየት ይቻላል።

14.ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን 3፡30 ሰዓት ከጥዋቱ ታሽጎ 4፡00 ከጥዋቱ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በከተማ ሰቲት ሁመራ ማዘጋጃ ቤት ቢሮ ቁጥር 10 ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ያለመገኘት የጨረታውን ሂደት እያስተጓጎልም።

15 የጨረታው ዋጋ ፀንቶ የሚቆይበት ለ45 ቀናት ይሆናል።

16. ተጫራቾች የሚሞሉት ዋጋ ከነቫቱ መሆኑ እና አለመሆኑ ማመላከት አለባቸው።

17. ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች እቃውን በ 15 ተከታታይ ቀናት በጽሕፈት ቤቱ ግቢ ማስረከብ ይኖርበታል።

18. ጽሕፈት ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው።

19 ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 034 248 79 05/09 12 69 19 68 መደወል ትችላላችሁ።

የሰቲት ሁመራ ከተማ ማዘጋጃ ፅህፈት ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo