የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በጤና ጥበቃ ቢሮ የተለያዩ ህክምና ተቋማት የሚውሉ የህክምና ቁሳቁሶች፣ የተለያዩ አይነት ህትመት ግዥ ለመግዛት ህጋዊ ከሆኑ አቅራቢዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

የኣፋር ጤና ጥበቃ ቢሮ
  • የተለያዩ ህክምና ተቋማት የሚውሉ የህክምና ቁሳቁሶች
  • የተለያዩ አይነት ህትመት ግዥ                                                                                         
    1. በዚህ ግልፅ ጨረታ የሚወዳደሩ አቅራቢ ድርጅቶች በ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት የታደሰ የንግድ ፍቃድ የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለበት።
    2. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የመወዳደሪያ ሀሳብ ኦርጂናሉን በአንድ ፖስታ ኮፒውን በአንድ ፖስታ የተጫራቾች ስምና ፊርማ አድራሻ በግልፅ ተፅፎባቸው ሁለቱም ፖስታዎች በአንድ ፖስታ ተደርጎ በሰም ታሽጎ መቅረብ ሲኖርበት ለህክምና ተቋም አገልግሎት የሚውል የህክምና ቁሳቁሶችና ህትመት ለሚጫረቱት የህክምና ቁሳቁሶችና ህትመት አይነት እና መጠን ስዕላዊ መግለጫ የሚያስፈልገው በከለር የታተመ ስዕላዊ መግለጫ በፖስታ ውስጥ ተደርጎ በተወሰነው ጊዜና ሰዓት በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ጥበቃ ቢሮ በግዥናፋይ/ንብ/አስ/ደጋ/ስራ ሂደት ህንፃ ቁጥር 1 ለዚሁ ተብሎ የተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
    3. ተጫራቾች የሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ቢሮው ለመግዛት የፈለገውን የህክምና ቁሳቁሶችና ህትመት ግዥ ለእያንዳንዳቸው ለሚገዙት እቃዎች ለብቻቸው አንድ ኦርጂናል እና አንድ ኮፒ የመወዳደሪያ ሰነድ ማቅረብ ወይም የመጫረቻ ሰነድ መምጣት ግዴታ አለባቸው።
    4. የሚገዙት እቃዎች አይነት እና ዝርዝር መግለጫ (specification )ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል።
    5. ማንኛውም የጨረታ ተወዳዳሪ ለሚያቀርባቸው እቃዎች ቫት ሳይጨምር የጠቅላላ ዋጋው ነው 1% የጨረታ ማስረከቢያ ቢድ ቦንድ ወይም (CPO) ከመወዳደሪያ ሃሳብ ማቅረቢያ ጋር በፖስታ ታሽጎ ማቅረብ አለበት።
    6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00(አንድ መቶ ብርከፍለው ለአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የጤና ጥበቃ ቢሮ በግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ደጋ/ስ/ሂደት ህንጻ ቁጥር መውሰድ ይችላሉ።
    7. የተዘጋጀው የጨረታ ዝርዝር ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ለተከታታይ 10(አስር) የስራ ቀናት በአየር ላይ ውሎ በ11 ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት የጨረታው ሳጥን ተዘግቶ በዛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች በባለቤት ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ጥበቃ ቢሮ በግዥ/ፋይ/ንብ/አስ/ደጋ/ስራ/ሂደት ህንፃ 1 ይከፈታል።
    8. ተጫራቾች ሰነዱን ገዝተው በመሙላት እና በማዘጋጀት ኦርጂናል የመወዳደሪያ ሀሳብ ዶክመንታችሁን በአንድ ፖስታ ውስጥ በሰም በማሸግ ኮፒውን በሌላ ፖስታ ውስጥ በሰም በማሸግ በማስገባት ሁለቱንም ፖስታዎች በአንድ ፖስታ አድርጎ በሰም አሽገው ለዚሁ ግዥ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በስም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
    9.  ቢሮው ሊገዛ ያቀረበው የእቃ ዝርዝር ተጫራቾች የህክምና ቁሳቁሶችና ህትመት በከለር የታተመ ስእላዊ መግለጫ ማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
    10. አሸናፊው ድርጅት የአሸነፈበትን እቃዎች ወይም አገልግሎቶች የመትከል እና የመግጠም ግዴታ አለባቸው።
    11. ሻጭ ንብረቱን በንብረት ክፍል ድረስ ወስዶ ካስረከበ በኋላ በስሙ ሞዴል 19 አስቆርጦ ሂሳብ ክፍል ወስዶ ማወራረድ አለበት።
    12. የጨረታው መክፈቻ ጊዜ ቀን የጨረታውን መክፈቻ ፕሮግራሙን ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙ ሲቀሩ የጨረታውን መክፈቻ ሂደት አያስተጓጉሉም::
    13. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
    በተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለጎት አፋር/ብ/ክ/መንግስት ጤና ጥበቃ ቢሮ
    በስልክ ቁጥር ፡-033-666-00-21 ደውለው ይጠይቁ
    የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በጤና ጥበቃ ቢሮ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo