በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ

በጨረታዉ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ድርጅቶች ሆነ ግለሰብ ከዚህ በታች የተገለፀዉን መመሪያዎች ግዴታዎች ማማላት አለባቸዉ

1 ዕቃዎቹን ለመግዛት የሚጫረት ማንኛዉም ድርጅት ሆነ ግለሰብ ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 10681 በስፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለበት

2 ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸዉ የዘመኑ ግብር መክፈላቸዉን ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አላበቸዉ

3 ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸዉ እያንዳንዱ ያገለገሉ ዕቃዎች ዋጋ በማስቀመጥ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ በግልፅ መፃፍ ይኖርባቸዋል

4 ዕቃዎቹ በሚገኙበት ቦታ በመገኘት የሚሸጡትን ዕቃዎች ዝርዝር ሁኔታ መመልከት ይችላሉ ዕቃዎቹ የሚገኙበት ቦታ ሽሬ እነዳስላሴ ማእከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ሽሬ እንዳስላሴ ማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላላ መምሪያ ሱር ካምፕ ሽረ እነዳስላሴ ማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ጉና ድፕ

5 ጨረታዉን ያሸነፈ ድርጅትም ሆነ ግለሰብ ዕቃዎችን በ15 ቀናት ዉስጥ ሙሉ በሙሉ አጠቃሎ ማንሳት አለበት

6 ጨረታዉ ያሸነፈ ድርጅትም ሆነ ግለሰብ በተጠቀሰዉ የጊዜ ገደብ ዉስጥ ዕቃዎችን አጠቃሎ ካላነሳ በየቀኑ 300 ብር ቅጣት ይከፍላል

7 የጨረታ ሰነዱን ከተጫራቾች ዝርዝር መመሪያ ጋር የማይመለስ ብር 100 ብር በመክፈል ይህ ማስታወቂያበጋዜጣ ታዉጆ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ሰዓት ባሉት ቀናት ዉስጥ ሽሬ በሚገኘዉ የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ንብረት ቡድን ቢሮ መግዛት ይችላል

8 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸዉን ሽሬ ከተማ በሚገኘዉ ማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላላ መምሪያ መዝናኛ ክበብ ዉስጥ ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል

9 ጨረታዉ መጋቢት 10/7/2010 ዓም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ 4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ድርጅት

10 አሸናፊ ድርጅቶች ሆነ ግለሰብ ዉል ሲፈፅሙ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና በባንክ የተረገጋጠ ስፒኦ ወይም ጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል

11 መስሪያ ቤቱ የተሸላ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ጨረታዉን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

በስልክ ቁጥር 034 244 00 11 0910354733