የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር -2/2017ዓ/ም
በትግራይ ክልል ትግራይ መገናኛ ብዙኃን ኤጀንሲ ግዥና ንብረት ኣሰተዳደር ለ2017 በጀት ዓመት የዲስክቶፕ ኮምፒተር በሃገር ኣቀፍ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ኣለባቸው።
➢ የ2017ዓ/ም ህድሳት የተደረገለት ንግድ ፍቃድ፣ የኣቅራቢነት ምዝገባ ሰርቲፊኬት ቲን ምዝገባ ወረቀትን የጥቅምት ወር 2017 የቫት ዲክላሬሽን ማቅረብ ኣለባቸው
➢ መስፈርቶቹን የሚያሟሉ ሁሉም ተጫራቾች ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15(አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 400.00 ( ኣራት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነድ ከትግራይ መገነኛ ብዙኃን ኤጀንሲ ግዥና ንብረት ኣሰተዳደር ቢሮ ቁጥር 105 ከቀን 27/05/2017 ዓ/ም እስከ 11/06/2017 ዓ/ም ከቀኑ 11:30 ድረስ በስራ ሰአት ሰነዶችን መግዛት ትችላላቹ ።
➢ ጨረታው የሚዘጋበት የመጨረሻ ቀን 12/06/2017ዓ/ም ከጥዋቱ 4:00 ሰኣት ላይ ተዘግቶ ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በተመሳሳይ ቀን 12/06/2017ዓ/ም ጥዋት 4:30 ቢሮ ቁጥር 105 ይከፈታል።
➢ የጨረታማስከበርያ/ዋስትና/ በተጫራቶች ምርጫ ከሚከተሉት ዓይነቶች አንዱ ሊሆን ይችላል።
ሀ. በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና፤
ለ. በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና፤
ሐ. በአር ውስሠ ባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የክፍያ ትዕዛዝ ሁኖ 30,000.00(ሰላሳ ሺ ብር) ማስያዝ ኣለባቸው።
➢ የሚያሰፈልጉት የደኩመንት ብዛት ኦርጅናል ደኩመንት ከነ አንድ ኮፒ ለየብቻቸዉ በፖስታ በማሸግ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸዉ "
➢ ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ውስጥ ያሉትን ቅፆች በትክክል በመሙላት፣ በያንዳንዱ የሰነዱ ቅፅ ፈርማ እና የድርጅቱ ማሕተም ማድረግ ኣለባቸው።
➢ ድርጅታችን ትግራይ መገናኛ ብዙኃን ኤጀንሲ ይህ ጨረታ በማንኛውም ግዜ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ይሁን በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ኣድራሻ-ትግራይ መቐለ
ትግራይ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ
ቢሮ ቁጥር ----105 ግዥና ንብረት ኣስተዳደር
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር ----- 0342406380
ፋክስ ቁጥር 2510344402860