በአፈፃፀም ከሳሽ አቶ ግርማይ ተ/ሃይማኖት
እና
በአፈፃፀም ተከሳሽ ወ/ሮ ፀጋ ገ/ታትዮስ
በመካከል ባለው የአፈፃፀም ክርክር በመቐለ ከተማ በክፍለ ከተማ ሰሜን ላጪ የሚገኝ ቤት እና ቦታ ስፋቱ 219.6 ካሬ ሜትር የሆነ ቤት እና ቦታ አዋሳኙ በምስራቅ 007B፣ በምዕራብ መንገድ፣ በደቡብ ክፍት ቦታ፣ በሰሜን 006 በጨረታ መነሻ ዋጋ 439,250.16 (አራት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ሺህ ሁለት መቶ ሃምሳ ከአስራ ስድስት ሳንቲም) ሊያጫርት ስለተፈለገ በጨረታው ሊሳተፍ የፈለገ ጨረታው በሚካሄድበት ቀን በ17/6/2017 ዓ.ም ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ 6:30 ሰዓት ድረስ ቀርቦ እንዲጫረት እና የጨረታ አሸናፊው ለጊዜው 25% የሚያስይዝ መሆኑ የቀረውን ደግሞ በ15 ቀን ውስጥ ገቢ የሚያደርግ መሆኑ የጨረታው ውጤት ቀን 17/6/2017 ዓ.ም 9:00 ሰዓት እንዲቀርብ መቐለ የከተማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዟል፡፡
የመቐለ ከተማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት