የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ

የኢትዩያ ንግድ ባንክ ጎንደር ዲስትሪክት

የጨረታ ማስታወቂያ

ለመጀመሪያ ጊዜ ለሓራጅ የቀረበ

ከኢትዩßያ ንግድ ባንክ ጃንተከል ቅርንጫፍ ተበዳሪ የሆኑት አቶ አብርሃም ብርሃኑ ገ እየሱስ የተበደሩትን ገንዘብ በብድር ዉሉ መሠረት በወቅቱ መመለስ ባለመቻላቸዉ ለብድሩ መክፈል በመያዣነት የሰጡትን በባለቤታቸዉ በወ/ሮ ሂወት ተወልደ መሃሪ ስም የተመዘገበ እና የመረጋገጫ ሰነድ ቁጥር 19990/ 01/ 7285 ተመዝገቦ የሚገኘዉን በመቀሌ ከተማ ወረዳ ሰሜን ቀበሌ 11 የቤት ቁጥር አዲስ G+1 ለመኖሪያ የሚሆን የቦታዉ ስፋት 140 ካሜ የሆነዉን በግምት መነሻ ብር 779 ,579. 82 (ሰባት መቶ ሰባ ዘጠኝ ሺ አምስት መቶ ሰባ ዘጠኝ ብር ከሰማኒያ ሁለት ሳንቲም ) ህዳር 10 ቀን 2007 ዓ/ም ከጥዋቱ 3-6 ሰዓት ባንኩ በአዋጅ /ቁ 97/ 90 እና 216/ 92 በተሰጠዉ ስልጣን መሠረት በግልፅ ሐራጅ ጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል::

ስለዚህ ቤቱን በጨረታ ለመግዛት የሚፈልግ ማንኛዉም ግለሰብ ወይም ድርጅት በጨረታዉ ቀን በመገኘት መጫረት ይችላሉ::

ማሳሰቢያ-:

1 ተጫረቾች ለጨረታ ሲቀርብ የቤቱን ግምት መነሻ 1/4ኛ (ሃያ አምስት ፐርሰንት) በኢትዩያ ንግድ ባንክ ጃንተከል ወይም መቀሌ ቅርንጫፍ በሲፒኦ ማስያዝ ወይም በጨረታዉ ቀን በጥሬ ገንዘብ ይዘዉ መቅረብ አለባቸዉ::

2 በጨረታዉ የተሸነፉ ሰዎች ለጨረታ ያስያዙት ገንዘብ ወዲያዉኑ ይመለስላቸዋል::

3 የጨረታዉ አሸናፊ ቀረዉን ገንዘብ በ 15 (በእስራ አምስት) ተከታታይ ቀናት ዉስጥ አጠቃለዉ መክፈል አለባቸዉ ባይከፍሉ ግን የሐራጅ ዉጤቱ ተሰርዞ ያስያዙት ገንዘብ አይመለሰም ባንኩም ቤቱን እንደገና በጨረታ የመሸጥ መብቱ የተጠበቀ ነዉ::

4 ጨረታዉ የሚካሄደዉ በመቀሌ ከተማ ቤቱ በሚገኝበት ቦታ ነዉ::

5 ባንኩ በብድር መመሪያ መሠረት የሚጠይቀዉን መስፈርት አማልቶ ለሚቀርብ የጨረታ አሸናፊ ብድር የሚገኝበትን ሁኔታ ሊያመቻች ይችላል::

6 በሽያጭ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ የሚታሰብና ገዥ የሚከፍል መሆኑን እንገልፃለን::

7 ዝረዝር መረጃ ለማግኘት ወደ ኢትዩßያ ንግድ ባንክ ጎንደር ዲስትሪክት ጽቤት ወይም ጃንተከል ቅርንጫፍ በኣካል በመምጣት መጠየቅ ወይም በስልክ ቁጥር 0581114026 , 0581110261 , 0581112444 ደዉሎ መጠየቅ ይቻላል::

8 ባንኩ የተሻለ አማራጭ መንገድ ካገኘ ጨረታዉን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ ::

ማስታወቂያዉን ጥቅምት 6 ቀን 2007 ዓም ከወጣዉ አዲስዘመን ጋዜጣ ማየት ይችላሉ::