የፕሮፎርማ ማስታወቅያ(Shopping)
የመቀሌ ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ፅሕፈት ቤት ለመቀሌ ከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራምን ኣገልግሎት የሚዉሉ የተለያዩ ኣይነት የድህንነት መጠበቅያ እቃዎች እንዲሁም የእጅ መሳርያ(Hand tools ) እቃዎች በፕሮፎርማ ኣወዳድሮ መግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መስፈርቶች የምታማሉ ነጋዴዎች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል ፡፡
ተፈላጊ መስፈርቶች
1. የዘመኑ የታደሰ ንግድ ስራ ፍቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ፣ የኣቅራቢነት ምዝገባ ሰርቲፊኬት ፣ የቫት ምዝገባ ሰርቲፊኬት ፣ የቅርብ ወር ሻት ሪፖርት ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ ።
2. የመወዳደሪያ ሀሳቡ ከ 05/05/2017 ዓ/ም እስከ 12/05/2017 ዓ/ም ሰአት3:30 ለተጫራቾች ክፍት ሁኖ የሚቆይ ሲሆን በዚህ ቀን 3:30 ተዘግቶ 4:00 ሰዓት ቢሮ ቁጥር 033 ይከፈታል።
3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና
➢ የድህንነት መጠበቅያ እቃዎች ብር 150,000 (ብር ኣንድ መቶ ኣምሳ ሺ ብር ብቻ
➢ የእጅ መሳርያ እቃዎች 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)በCPO ፣ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ኣለባቸው " የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ጨረታው ከተከፈተበት ግዜ አንስቶ ለ15 ቀናት ይሆናል ።
4. የእቃዎች ማስረከብያ ቦታ በመስራቤታችን ግምጃ ቤት ሆኖ ማስረከብያ ግዜው ግዢው ከታዘዘበት ቀን ጀምሮ በ15 ቀናት ውስጥ ይሆናል ።
5. ኣቅራቢዎች ጠቅላላ ዋጋውን በቁጥርና በፊደል መፃፍ ኣለባቸው ፡፡ በቁጥር እና በፊደል በተገለፀው የዋጋ መጠን መካከል ኣለመጣጣም ካለ በፊደል የተገለፀው ተቀባይነት ይነረዋል ፡፡ በነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ መካከል ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋው ተቀባይነት ይኖረዋል።
6. ኣቅራቢዎች በእያንዳንዱ የዕቃ ዝርዝር ማቅረብያ ሰንጠረዥ ውስጥ የዕቃውን ኣይነትና ብዛት ፣ ነጠላ ዋጋ ፣ እና ጠቅላላ ዋጋውን መሙላት እንዲሁም ቀን ፣ ፊርማና የድርጅቱ ማህተም ማስፈር ይገባቸዋል ፡፡
7. ለአሸናፊ ተጫራቾች ዕቃውን ሙሉ ለሙሉ በውለታ መሰረት ኣጠናቅቆ ማስገባቱና ማጠናቀቁ ከተረጋገጠ በኋላ ቢበዛ በ7 ቀናት ውስጥ ሙሉ ክፍያ ይከፈለዋል ፡፡
8. ተጨራቾች የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ታክስን የሚያካትትና የማያካትት መሆኑን መግለፅ አለበት " ታክስን በትክክል ካልተገለፀ የቀረበው ዋጋ ታክስ እንዳካተተ ተቆጥሮ ውድድሩ ይካሄዳል "
9. አሸናፊ አቅራቢ የሚለየው ለተጠቀሱት ዕቃዎች በድምር እዕቃ ዝቅተኛ ዋጋ ኣቅራቢ ( LOT based) ይሆናል ።
10. ግዢ ፈፃሚው መ/ቤት ከአሸናፊ ድርጅት ጋር ውለታ ከመፈራረሙ በፊት የዕቃዉን ጠቅላላ ብዛት እስከ 20% (ሃያ ፐርሰንት) ጨምሮ ወይም ቀንሶ መፈራረም ይችላል ፡፡
11. ማንኛውም ተጫራች ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰአት በፊት የዋጋ ማቅረቢያው ሰነዱን /የመወዳደርያ ሀሳብ / ማስገባት ይኖርበታል ፡፡ ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰአት በኋላ የቀረበ የዋጋ ማቅረብያ ሰነድ /የመወዳደርያ ሀሳብ /ተቀባይነት የሌለው ሲሆን ኢንቨሎፑ ሳይከፈት ለተጫራቹ ተመላሽ እንዲሆን ይደረጋል።
12. ጨረታው የቴክኒክ መስፈርቱን ካማሉት ኣቅራቢዎች መካከል ዝቅተኛ ዋጋ ላቀረበው ተጫራች ኣሸናፊ ይደረጋል። ከሰላምታ ጋር
0344-406747/0344-408501/0344-406839