ቢሮ ሕርሻን ገጠር ልምዓትን

የፕሮፎርማ ግዢ ማሰታወቅያ

በግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የአፍሪካ ቀንድ የስደተኞች ተፅእኖ ምላሽ ልማት ፕሮጀክት ምዕራፍ ሁለት/ DRDIP-2 / በ 2016 ዓ/ም በያዘው በጀት መሰረት የ DRDIP-2 መኪና ታ.ቁ ኢት 4-15294 ሞዴል Kun 25L እና የቢሮ ሃላፊ ታ.ቁ ኮድ 4-02343 ሞዴል ባይክ × 25 መኪናች ለሆኑት አገልግሎት የሚውሉ የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎችና ጎማ ከታች በሰንጠረዡ ውስጥ የተጠቀሱት ዕቃዎች መግዛት ስለሚፈልግ የመወዳደርያ ሀሳብ እንድታቀርቡ ይጋብዛል፡ መስራያ ቤታችን ግዢውን የሚፈፅመው በጥራትም ሆነ በዋጋ ብቁ መሆናችውን አረጋግጦ የመረጣቸውን ይሆናል።


የዕቃዎች ዓይነትና ዝርዝርመግለጫ/እስፔሲፊኬሽንመለክብዛትprice Unit የአንድ ዋጋTotal Price ጠቕላላ ዋጋማብራርያ
1Shock Absorber F.R48510 – 09j20PCS01Kun 25L Model
2Shock Absorber R.R48531 – 09550PCS01Kun 25L Model
3Dinamo ( Wiper Moter )For Kun 25LPCS01Kun 25L Model
4Tire tubless205 – 50R16pcs05Model ባይክ × 25
5Pad kitF.RSET01Model ባይክ X 25
6Pad kitR.RSET01Model ባይክ X 25
7Oil Filterባይክ × 25pcs01Model ባይክ X 25
8Motor Oil#40Liter10Model ባይክ X 25
Total price of the Lot(የሁሉም እቃዎች የቀረበ ጠቕላላ ዋጋ)ይቀመጥ
በፊደል ብር(__)

1. ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ለመሳተፍ የሚያስችላቹ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/፣ ለቫትተመዝጋቢዎች የቫት ምዝገባ ሰርቲፊኬትና ፣ በመንግስት ግዢ ለመሳተፍ የተ ሰጠ ፍቃድ ፣የሁሉም ማሰረጃዎች ፎቶ ኮፒ መያያዝ አለበት

2. የመወዳደርያ ሃሳቡ በታሸገ ኢንቨሎፕ ሆኖ እስከ 24/10/2016 ዓ/ም ጥዋት 3፡00 ሰዓት ለቢሯችን የግዢ ቡድን ቢሮ ቁጥር 12 መድረስ አለበት። ፕሮፎርማው ሰኔ 24/2011 ጥዋት 3፡00 ተዝግቶ 3፡30 ይከፈታል።

3. የእቃው ማስረከብያ ቦታ በቢሯችን በሚገኘው ንብረት ክፍል ሆኖ ማስረከብያ ግዜው ግዢው ከታዘዘበት ቀን ጀምሮ በ 02 ተከታታይ ቀናት ይሆናል፡፡

4. አቅራቢዎች ጠቅላላ ዋጋውን በቁጥርና በፊደል መጻፍ አለባቸው፡፡ በቁጥርና በፊደል በተገለፀው የዋጋ መጠን ልዩነት ካለ በፊደል የተገለፀው ተቀባይነት ይኖረዋል፡፡ በነጠላ ዋጋና በጠቅላላ ዋጋ መካከል ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋው ተቀባይነት ይኖረዋል፡፡ የመወዳደርያ ሂሳቡ ዋጋ የሚቀርበው በኢትዮጵያ ብር ይሆናል።

5. አቅራቢዎች በእያንዳንዱ የዕቃ ዝርዝር ማቅረብያ ሰንጠረዥ ውስጥ የዕቃው ዓይነትና ብዛት፣ነጠላ ዋጋ፣እና ጠቅላላ ዋጋውን መሙላት እንዲሁም ቀን ፣ ፊርማና የድርጅቱን ማህተም ማሰፈር ይገባቸዋል፡፡

6. ለአሸናፊ ተጫራች ዕቃውን ሙሉ ለሙሉ በውሉ መሰረት አጠናቆ ማስገባቱና ጥራቱ ከተረጋገጠ በኃላ ቢበዛ በሰባት ቀናት ውስጥ ሙሉ ክፍያ ይከፈለዋል።

7. የመወዳደርያ ሀሳብ ማቅረብያ ቋንቋው በአማርኛ ነው፡፡

8. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ታክስን የሚያካትትና የማያካትት መሆኑ መግለፅ አለ ባቸው።ታክስ በትክክል ካልተገለፀ የቀረበው ዋጋ ታክስ እንዳካተተ ተቆጥሮ ውድድሩ ይካሄዳል፡፡

9. አሸናፊ አቅራቢ የሚለየው ለእያንዳንዱ ዕቃ ያቀረበው ( Item by Item) ዝቅተኛ ዋጋ ያቀረበ መሰረት ይሆናል፡

10. ግዢ ፈፃሚው መስራቤት ከአሸናፊው ድርጅት ጋር ውል ከመፈረሙ በፊት የዕቃውን ጠቅላላ ብዛት እስከ 15 %( አስራ አምስት ፐርሰንት) ጨምሮ ወይም ቀንሶ መፈራረም ይችላል፡

11. ማንኛውም ተጫራች ከጨረታ መዝግያ ቀንና ሰዓት በፊት የዋጋ ማቅረብያው ሰነዱን/የመወዳደርያ ሃሳብ/ ማስገባት ይኖርበታል ። ከጨረታ መዝግያ ቀንና ሰዓት ሰዓት በኃላ የቀረበ የዋጋ ማቅረብያ ሰነድ የማወዳደርያ ሃሳብ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን ኢንቨሎፑ ሳይከፈት ለተጫራቶች ተመላሽ ይሆናል።

12. ጨረታው የቴክኒክ መስፈርቱን/ ዝርዝር መግለጫውን/ ካሟሉት አቅራቢዎች መካከል ዝቅተኛ ዋጋ ላቀረበው ተጫራች ኣሸናፊ ይደረጋል።

13. መስርያ ቤታችን ፕሮፎርማው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡