በዓል መዚ ልማዓት እቶት ኢትዮጵያ

ለ3ተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 08/2016

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅ/ፅ/ቤት በኮንትሮባንድ ከአገር ሊወጣ ሲል ተይዘው ና ተወርሰው የሚገኝ የአፈር ማዳበሪያ ባለበት ሁኔታ ለዩኔን ህብረት ስራ ማህበራት ብቻ መንግስት ባወጣው ዋጋ ተመን መሸጥ ይፈልጋል፡፡

1. በመሆኑ ቅ/ፅ/ቤቱ ባወጣው የዕቃ ሽያጭ ጨረታ መወዳደር የሚፈልግ ማንኛው ተጫራች ፦

ሀ) በዘርፉ የፀና የንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ መሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችል፡፡

ለ) የዚህ አንቀፅ ፊደል ተራ (ሀ) ድንጋጌ ቢኖርም ለጨረታ የቀረቡ ዕቃዎች ግምታዊ ዋጋቸው 500,000 (ከአምስት መቶ ሺ ብር) በታች ከሆኑ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርቲፊኬት ማቅረብ አይገደድም፡፡

2. ተጫራቾች የሓራጅ ጨረታ ሰነድ ከማክሰኞ ሚያዝያ 13 ቀን 2016ዓ/ም ጀምሮ እስከ ቅዳሜ 17 ቀን 2016ዓ/ም የማይመለስ ብር 100(አንድ መቶ ብር) በመክፈል በቅ/ጽ/ቤቱ በመገኘት የጨረታ ሰነዱ መግዛት ይችላሉ፡፡

3. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ የዕቃውን የጨረታ መነሻ ዋጋ አምስት በመቶ (5%) ዋስትና CPO በመቐለ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማስያዝ

4. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡

ቅ/ጽ/ቤቱ ምየንብረቱ ዓይነትጨረታው ዓይነትየንብረት መመልከቻ ሰነድ ከወሰዱ ቀን ጀምሮየጨረታው መክፈቻ ቀን ና ሰዓት
እስከ
መቐለ ቅ/ጽ/ቤትማዳበሪያሃራጅ ጨረታ13/09/201617/09/16 ከቀኑ 5፡0017/09/2016 ዓ.ም ከቀኑ 5:15 ጀምሮ

5. የጨረታ መክፈቻ ቦታ መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የሚካሄድ ሲሆን ጨረታው

ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡

6. ለጨረታ አሸናፊዎች ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ወስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል፡፡

7. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ለማሸነፉ ከተገለጸለት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፈበት ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡

8. ከላይ በተ/ቁ 7 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ ይቀርባል::

9. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን