የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡- ERMMB/NCB/007/2017 E.C
የኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር መቐለ ቅ/ፅ/ቤት ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የሚከተሉትን እቃዎች ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡-
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር፡- ERMMB/NCB/007/2017 E.C
- ሎት አንድ- የሰዓት መቆጣጠሪያ የጣት አሻራ ማሽን (Biometric Attendance) በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የእቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ፤
- ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር ባለስልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
- ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ያላቸው፤
- የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ የሰዓት መቆጣጠሪ የጣት አሻራ ማሽን (Biometric Attendance) ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ) እያንዳንዳቸው በባንክ በተመሰከረለት ቼክ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200.00 (ሁለት መቶ ብር) ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ አጠገብ የሚገኘው የትግራይ ክልል አካል ጉዳተኞች ማህበር ህንፃ ከሚገኘው የቅ/ጽ/ቤቱ ግዥ ቡድን ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 20 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 08 ቀን 2017 ዓ.ም በ4፡00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታውም በዚሁ ዕለት በ4፡30 ሰዓት በመስሪያ ቤቱ አዳራሽ አራተኛ ፎቅ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- የጨረታው አሸናፊ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና 10% (አስር በመቶ) CPO በማስያዝ ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማል።
- መ/ቤቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች ሁሉም ቫት ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባቸዋል፤ ተጫራቾች ዋጋው ከነቫቱ መሙላት ይጠበቅባቸዋል።
- ማንኛውም ስርዝ ድልዝ ያለበት የጨረታ ሰነድ ከጨረታ ውጪ ይደረጋል።
- የሰዓት መቆጣጠሪ የጣት አሻራ ማሽን (Biometric Attendance) ሙሉ specification የያዘ ሰነድ በጨረታ ሰነድ ላይ መሆኑን እናሳውቃለን።
- ስልክ ቁጥር፡- 034-441-1005/ 09-35-28-22-74/ 09-34-34-52-98 ፋክስ፡- 034-440-7309
የኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር መቐለ ቅ/ፅ/ቤት